የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል | ከይር ታይምስ
አምዶች
የቅርብ ዜና
የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ
ፖለቲካ / ምርጫ

የብልፅግና ፓርቲ በቁልፍ ክልሎች አሸነፈ፤ ከፊል የምርጫ ውጤቶች ይፋ ሆነዋል

በያፌት ግርማ | July 4, 2026

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ22 የምርጫ ክልሎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለክልል ምክር ቤት የቀረቡ ዕጩዎችን ውጤት ይፋ ማድረጉን አስታወቀ። ቦርዱ ውጤቱን ይፋ ያደረገው ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ በስካይ ላይት ሆቴል በሚገኘው ጊዜያዊ ጣቢያው በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

በዚሁ መግለጫ መሠረት ቦርዱ ከአማራ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአንድ፣ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሦስት፣ ከኦሮሚያ ክልል ለክልል ምክር ቤት ዘጠኝ እና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰባት፣ እንዲሁም ከሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት በሁለት የምርጫ ክልሎች ላይ የቀረቡ ዕጩዎችን ውጤት በይፋ አሳውቋል።

የምርጫ ውጤቱን ዝርዝር በተመለከተ፤ በአማራ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመወዳደር በጎንጎን ምርጫ ክልል የብልፅግና ፓርቲ በብቸኛነት ዕጩውን ያቀረበ ሲሆን፣ ከፍተኛውን ድምፅ ማግኘቱ ተገልጿል። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሦስት ምርጫ ክልሎች ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል በሁሉም ምርጫ ክልሎች የብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች ከፍተኛውን ውጤት ማግኘታቸው ተመልክቷል።

በተመሳሳይ ሁኔታ ቦርዱ በኦሮሚያ ክልል ለክልል ምክር ቤት በዘጠኝ እና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰባት የምርጫ ክልሎች መካከል ባካሄደው ውድድር፤ በሁሉም የክልል እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎች የብልፅግና ፓርቲ ዕጩዎች ከፍተኛ ውጤት ማግኘታቸውን በመግለጫው አስታውቋል።

በሌላ በኩል በሶማሌ ክልል ለክልል ምክር ቤት ዕጩ በቀረበባቸው ሁለት የምርጫ ክልሎች፤ በሁለቱም አንደኛውን ከፍተኛ ውጤት የብልፅግና ፓርቲ ዕጩ ያገኘ ሲሆን፣ በሁለተኛው የምርጫ ክልል ደግሞ የኦጋዴን ነፃነት ግንባር (ኦነግ) በዕጩነት ያቀረባቸው ተወዳዳሪ አራተኛውን ከፍተኛ ውጤት ማግኘታቸውን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መግለጫ ያሳያል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ