የሕዝብ እንደራሴዎች ወይስ የፖለቲካ ምስጢረኞች? | ከይር ታይምስ
አምዶች
የቅርብ ዜና
የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ
ነፃ ሃሳብ / አስተያየት

የሕዝብ እንደራሴዎች ወይስ የፖለቲካ ምስጢረኞች?

ያፌት ግርማ | July 4, 2026

የፓርላማው የሚዲያ ከልከላ እና የዲሞክራሲው መጋረጃ መቀደድ

በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ውስጥ ፓርላማ የሕዝብ ድምፅ የሚሰማበት፣ የመንግሥት አሠራር የሚገመገምበትና ግልጽነት የሚነግሥበት የመጨረሻው የሕዝብ አምባ ነው። ነገር ግን በኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውስጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየታየ ያለው አካሄድ ከዚህ በተቃራኒው የቆመ ሆኗል። 

ምክር ቤቱ መደበኛና የቋሚ ኮሚቴ ስብሰባዎቹን ለግል መገናኛ ብዙሃን ዝግ በማድረግ፣ የሕዝብን መረጃ የማግኘት መብት በይፋ እየገደበ ይገኛል።

የሕግ የበላይነትን እናስከብራለን የሚሉ አካላት ራሳቸው የደነገጉትን ሕግ ጥሰው፣ ጋዜጠኞችን ከበር ሲያባርሩ ማየት አገሪቱ ወደ የትኛው የፖለቲካ አቅጣጫ እየተጓዘች እንደሆነ ማሳያ ነው።

በኢፌድሪ ሕገ-መንግሥት አንቀፅ 58 (5) እና በምክር ቤቱ የአሠራርና የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008 ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው፤ የምክር ቤቱ ስብሰባዎች በሙሉ በግልጽ መካሄድ አለባቸው። 

ስብሰባን ዝግ ማድረግ የሚቻለው በሕግ አስፈጻሚው ወይም በአባላት ተጠይቆ፣ ከግማሽ በላይ በሆነ የምክር ቤቱ አባላት ድምፅ ሲደገፍ ብቻ ነው።

አሁን ግን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም። ፓርላማው ለምን የግል ሚዲያዎችን እንደከለከለ በይፋ የሰጠው ማብራሪያም ሆነ ያስተላለፈው የውሳኔ ድምፅ የለም። ይህ የሚያሳየው ተቋሙ በሕግና አሠራር ሳይሆን፣ በጥቂት ግለሰቦች ፍላጎትና “ትእዛዝ” እየተመራ መሆኑን ነው።

አንዱን የመንግሥት ልሳን ፈቅዶ፣ የግል ሚዲያዎችን መከልከል ደግሞ አድሏዊነት ብቻ ሳይሆን፣ ነፃ ጋዜጠኝነትን የመቅበር ፍላጎት ነው።

ለመሆኑ በፓርላማው በር ላይ መጋረጃ እንዲጣል የተፈለገው ምን ምስጢር ስላለ ነው? ዝግ በተደረጉት ስብሰባዎች ውስጥ የተገመገሙት የገንዘብ፣ የጤና፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴሮች እንዲሁም የልማት ባንክ የዘጠኝ ወር ሪፖርቶች ናቸው። እነዚህ ተቋማት የሕዝብን ገንዘብና ጥቅም የሚያስተዳድሩ እንደመሆናቸው፣ አፈጻጸማቸው ለሕዝብ ግልጽ ሊሆን ይገባ ነበር።

ከዚህ የከፋው ተቃርኖ ግን “የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅ” በዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሲወያይበት፣ ውይይቱ ለግል መገናኛ ብዙሃን ዝግ መደረጉ ነው። መረጃን ስለመፍቀድ የሚመክር አዋጅ፣ መረጃን በመከልከል ሲጀመር ማየት እጅግ አስቂኝ እና አሳዛኝ ክስተት ነው።

ይህ አካሄድ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት መምህሩ አብዲሳ ዘርዓይ (ዶ/ር) ለሸገር ራዲዮ እንደገለፁት፦ “እኔ ከመረጥኳቸው ውጪ እዚያ አካባቢ ዞር አትሉም" ማለት የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት የሚሸረሽር ድርጊት ነው ብለዋል።

በዚህ መሀል እንደ ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ያሉ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አጋዥ ተቋማት ያሳዩት ዳተኝነት ሌላው የሚዲያውን ክንፍ የሰበረ ክስተት ነው።

ሸገር እንደዘገበው የእንባ ጠባቂ ተቋም “በደብዳቤ የደረሰኝ ቅሬታ የለም፣ ስለዚህ አልተከታተልኩም” ማለቱ የቢሮክራሲ ሰበብ እንጂ የኃላፊነት ስሜት አይደለም።

ኢሰመኮም በተመሳሳይ “ክትትል አላደረግኩም፣ አስተያየት አልሰጥም” በሚል እጁን አጣጥፎ መቀመጡን ሸገር ራዲዮ ነገሮናል። አገር አቀፍ የሚዲያ ከልከላ እየተካሄደ፣ ጋዜጠኞች ከፓርላማ በር ላይ እየተባረሩ፣ ተቋማቱ “ማስረጃ በደብዳቤ አልመጣልኝም” በሚል ሰበብ ዝምታን መምረጣቸው፣ የቁጥጥር ሥርዓቱ ምን ያህል እንደደነዘዘ ያሳያል።

በአጠቃላይ የዜጎች መብት አደጋ ላይ ነው። የመገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታምራት ኃይሉ እንዳሉት፤ መረጃ የማግኘት መብት ለጋዜጠኞች ብቻ ሳይሆን “ለሁሉም ዜጎች” የተፈቀደ ሰብዓዊ መብት ነው። ሚዲያዎችን መከልከል ማለት ሕዝቡ የላካቸው እንደራሴዎች ምን እየሠሩለት እንደሆነ እንዳያውቅ ዓይኑን ማወር ማለት ነው።

መንግሥት በሕግ የደነገገውን የመረጃ ነፃነት የማክበር ግዴታ አለበት። ፓርላማው የሕዝብ ተወካዮች መሰብሰቢያ መሆኑ ቀርቶ በጥቂት ባለሥልጣናት ፈቃድ ብቻ የሚንቀሳቀስ “የምስጢር ቤት” ከሆነ፣ የዲሞክራሲ ሥርዓቱ መሞቱን አውጆ መጋረጃውን ሙሉ በሙሉ መዝጋት ይሻላል። ካልሆነ ግን፣ ይህ ሕገ-ወጥ እገዳ በአስቸኳይ አንስቶ፣ የፓርላማው በር ለነፃ ጋዜጠኞች ክፍት ሊሆን ይገባል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ