ታዋቂው የባህላዊ ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ | ከይር ታይምስ
አምዶች
የቅርብ ዜና
የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ የመንገድ መሠረተ ልማት መስፋፋት የቱሪስት መዳረሻዎችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም ፋና ወጊ ሚና ይጫወታል ተባለ የቤት ግንባታ ማዳሪጃ ደንብ (ለመንግስት ሰራተኞች) በቀጥታ ስርጭት፦ የናሳ (NASA) ጠፈርተኞች ከአለም አቀፉ የጠፈር ጣቢያ ወጡ የባይደን ትችት የዲሞክራቶችን እና የሪፐብሊካኖችን የፖሊሲ ልዩነት በድጋሚ ያጎላ ነው ተባለ ከታገደው የኢራን 12 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ስድስቱ ሊለቀቅ ነው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዶ/ር ወንድወሠን አሠፋ መዝገብ ለተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ማደራጃ ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ; * የማረሚያ ቤት ኃላፊው ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዘ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 76ኛው ዙር የመመረቂያ በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አዲሱ የትምህርት ሪፎርም የሀገሪቱን መዋቅራዊ ስብራት ለመጠገን ወሳኝ መሆኑን ገለጹ አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የኢራንን ይዞታዎች አጋየች! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ኮሚሽን ለቀጣዩ ሀገራዊ ውይይት መነሻ የሚሆኑ ዋና ዋና አጀንዳዎችን ይፋ አደረገ
ዜና / የሀገር ውስጥ ዜና

ታዋቂው የባህላዊ ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

በያፌት ግርማ | July 4, 2026

የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ በተለይም የጎጃምን ለስላሳና ማራኪ ዜማዎች በማንጎራጎርና ለትውልድ በማሻገር የሚታወቀው አንጋፋውና ተወዳጁ አርቲስት ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፉ ተገለጸ።

አርቲስቱ ባደረበት ድንገተኛ ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በትላንትናው ዕለት በሰላም ማለፉን የቅርብ ቤተሰቦቹና የሙያ አጋሮቹ በታላቅ ሀዘን ገልጸዋል።

​አርቲስት ሰማኸኝ በለው በሀገራችን የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ በተለይ በባህላዊው ዘውግ ላይ የማይረሳ አሻራ ጥሎ ያለፈ ከያኒ ነው። የብዙዎቻችንን የልጅነት ጊዜ በትዝታ ወደኋላ የሚወስዱት፣ በገጠርም ሆነ በከተማ በሰፊው የሚደመጡትና ማህበረሰባዊ እሴትን የጠበቁ ስራዎቹ ዘመን የማይሽራቸው ነበሩ።

​"አፈር ለሚበላው ለሚበሰብሰው

ለዚህ ፈራሽ ገላ ቁምጣ መቼ አነሰው"

​እያለ ህይወትንና አለምን የሚመዝንባቸው ጥልቅ ፍልስፍና ያዘሉ ግጥሞቹና ዜማዎቹ ዛሬም ድረስ በሰዎች ልብ ውስጥ ህያው ሆነው ይኖራሉ። በከብት ጥበቃ፣ በደማቅ ሰርግና በተለያዩ ህዝባዊ በዓላት ላይ የሰማኸኝን ሙዚቃ ያልሰማ፣ አብሮ ያልጨፈረና ያላንጎራጎረ የለም ማለት ይቻላል። የባህላዊ የአማርኛ ሙዚቃ ሲነሳ ቀድመው ከአእምሯችን ከሚመጡት ጥቂት ከዋክብት መካከል አንዱ እርሱ ነበር።

​አርቲስት ሰማኸኝ በለው ከሙዚቃ ስራዎቹ ባሻገር በትህትናው፣ በሀገር ፍቅሩና ለባህል ባለው ታማኝነት በሚያውቁት ዘንድ ሁሉ እጅግ ይወደድና ይከበር የነበረ ድንቅ ሰው ነበር። ሞት የማይቀረው የሰው ልጅ ሁሉ እጣ ፈንታ በመሆኑ፣ የሚሆነው ካለመሆን አያመልጥምና እነሆ ስራዎቹንና ውብ ትዝታዎቹን ለህዝቡ አውርሶ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል።

​የአርቲስቱን ስርዓተ ቀብር አስመልክቶ የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን፣ የቀብሩ ስነ-ስርዓት የሚፈጸምበትን ጊዜና ቦታ በቀጣይ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ታውቋል።

​ከይር ታይምስ ለአርቲስት ሰማኸኝ በለው ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ለሙያ አጋሮቹና ለሙዚቃ አፍቃሪያን በሙሉ መፅናናትንና ጥልቅ ሀዘንን ይመኛል።

​ነፍስህ በሰላም ትረፍ ሰሜ ባላገሩ!

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ