አምዶች
የቅርብ ዜና
አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ በሃይማኖት ጉዳዮች እና ሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሙሉ መግባባት ተደረሰ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ የአንበሳ ባንክ ሙሉ በሙሉ አዲስ የዳይሬክተሮች ቦርድ መረጠ የመንግሥት “ዜሮ ተፈናቃይ” መርሐግብር እና የተሸፈኑ እውነታዎች የአሜሪካ በግብፅ ላይ ያተኮረ አካሄድ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂ እያበላሸው ነው — ብሌን ማሞ ዲሪባ አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ በሃይማኖት ጉዳዮች እና ሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሙሉ መግባባት ተደረሰ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ የአንበሳ ባንክ ሙሉ በሙሉ አዲስ የዳይሬክተሮች ቦርድ መረጠ የመንግሥት “ዜሮ ተፈናቃይ” መርሐግብር እና የተሸፈኑ እውነታዎች የአሜሪካ በግብፅ ላይ ያተኮረ አካሄድ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂ እያበላሸው ነው — ብሌን ማሞ ዲሪባ
ነፃ ሃሳብ / ትዝብት

የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ቀዳሚ ሀላፊነት የመንግስት አይደለምን?

በኤልያስ መሠረት | July 4, 2026
🔒 Log in or create an account to earn rewards for reading this article!

ይህ በምሥራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳና አካባቢው በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች እና በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት አስመልክቶ የቀረበው መረጃ፣ የሀገሪቱን ወቅታዊ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።

የሰሞኑ የምሥራቅ አርሲ ዞን የአሰኮ ወረዳ ዘገባዎች ልብን ያደማሉ፤ ህሊናን ያቆስላሉ። ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በአካባቢው በታጣቂዎች ተሰነዘረ የተባለው መጠነ ሰፊ እና እጅግ አሰቃቂ ጥቃት የንጹሃንን ሕይወት እየቀጠፈ፣ የሃይማኖት ተቋማትን እያነደደ ይገኛል። እስካሁን በተረጋገጠ መረጃ ብቻ የ49 ወገኖቻችን ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ማለፉ ታውቋል።

ከዚህ በላይ የሚያስደነግጠው ግን ቁጥራቸው ከ280 በላይ የሆኑ ዜጎች ያሉበት መሬት አለመታወቁ ነው። የስልክ መስመሮች ተቋርጠዋል፣ ፍለጋው ቆሟል፣ ቤተሰብ በስጋት ተውጧል። ነዋሪዎች በፍርሃትና በለቅሶ እየተናገሩ ያሉት አንድ መራራ እውነት አለ፦ "እነዚህ የጠፉት ሰዎች በሙሉ ተለቅመው ተገድለው ሊሆን ይችላል" የሚል የቁም ቅዠት የሆነ የጭንቅ ስጋት።

ይህ ጥቃት ድንገተኛ አደጋ አይደለም። የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚናገሩት የሸኔ ታጣቂዎች ከዚህ ቀደምም ‘ጠለታ ገብርኤል’ በሚባለው ስፍራ ከሰባት ጊዜ በላይ ተመሳሳይ የጥቃት ሙከራዎችን አድርገዋል። የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ግን የታጣቂዎቹ የተደራጀ የቁጥር ብልጫ እና የወረራው ስፋት ነው። ከመሪቲ ወረዳ፣ ከፈንታሌ፣ ከከረዩ እና ከኢቱ አካባቢዎች የተሰበሰቡ ወደ ሶስት ሺህ የሚጠጉ ታጣቂዎች በአንድነት በመተባበር በአሰኮ ወረዳና አካባቢው ላይ ዘምተዋል።

ቢዮ ቀበሌ፣ ጠለታ ገብርኤል፣ ኩፍቴና መድኃኔዓለም በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ በሳተና እሳት መጋየታቸውን ነዋሪዎች በስቅስቅ ለቅሶ እና በጩኸት እየገለጹ ይገኛሉ። ጥቃቱ በእሬቻ ሚካኤል፣ በሱንቴ ማርያም፣ በሌንጫ ኦዳ፣ በኳስ ድሬ፣ በአርባ ቀላ እና በወራንቡስ አካባቢዎች አሁንም ድረስ እንደሰደድ እሳት እየተስፋፋ ነው።

ነዋሪዎቹ እንደሚሉት እስካሁን ድረስ አንድም የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ወደ ስፍራው አልገባም። ታጣቂዎቹ አካባቢውን ከበው የሰው ማምለጫ ቀዳዳ በማጥበብ እንደ ከብት እየጨፈጨፉት ይገኛሉ። ይህ አካባቢ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትውልድ ስፍራ እንደሆነ ይነገራል። ምናልባትም ዛሬ ሕይወታቸው ካለፈው ንጹሃን መካከል አብረዋቸው የተማሩ፣ ያደጉ፣ ወይም በቅርብ የሚያውቋቸው የልጅነት ጓደኞቻቸው ሊኖሩ ይችላሉ።

በሌላው ዓለም እንዲህ ዓይነት ታሪክ የማይረሳው ጥፋት ሲከሰት መሪዎች በፍጥነት ወደ ስፍራው አቅንተው ሕዝቡን ያጽናናሉ፣ የመፍትሔ አካል ይሆናሉ። በአሰኮ ወረዳ በቀጠለው ከበባ ምክንያት ወደ ስፍራው መሄድ አልተቻለም እንበል፤ ታዲያ በገዛ ትውልድ መንደር እንዲህ ዓይነት አሰቃቂ ጭፍጨፋ ሲፈጸም ‘ነፍስ ይማር’ ለማለት፣ ወይም ድርጊቱን በይፋ ለማውገዝ ምነው የከንቲባዋም ሆነ የሌሎች ባለሥልጣናት አንደበት ተሳሰረ? ለምንስ ዝምታን መረጡ?

ጥያቄው የባለሥልጣናትን የሃዘን መግለጫ ብቻ የሚመለከት አይደለም፤ የሀገርን ሕልውና እና የዜጎችን የመኖር መብት የሚወስን እንጂ። የሀገሪቱ ታላቅ መከላከያ ሠራዊት፣ ፌደራል ፖሊስ፣ የክልል ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻና ዘመናዊው የአየር ኃይል ተገንብተው የቆሙት ለምንድን ነው? ለሰዓታት ሳይሆን ለቀናት ሙሉ በአንድ ወረዳ ላይ የሚፈጸምን የተደራጀ ጥቃት መክተትና ንጹሃንን መታደግ ለምን ተሳናቸው? የደህንነት መዋቅሩ አስቀድሞ መረጃ ማግኘት እንዴት አቃተው? ወይስ መረጃው እያለ የመከላከል ፍላጎት አልነበረም? እነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ካላገኙ የሕዝብ በመንግሥት ላይ ያለው እምነት ሙሉ በሙሉ መናጋቱ አይቀሬ ነው።

የዚህች ሀገር ነገር አንዳንዴ ሰውን እጅግ ያደክማል፣ ተስፋም ያስቆርጣል። እውነቱን የያዘው አካል ታሳሪ፣ ንጹሃንን የጨፈጨፈው ታጣቂ ደግሞ በነጻነት የሚንሸራሸርባት ሀገር ሆናለች።

ይህንን መራራ እውነት ጽፎ ለሕዝብ ማጋራት የውስጥን እረፍት ባይሰጥም፣ ቢያንስ የህሊናን ዕዳ ለመክፈል ይረዳል። ይሁን እንጂ በድንጋጤና በለቅሶ ድምፃቸው እየተንቀጠቀጠ ያናገሩኝ የአሰኮ ወረዳ ዜጎች ምስልና ድምፅ መቼም ቢሆን ከአእምሮ የማይፋቅ ዘግናኝ የህይወት ጠባሳ ሆኖ ይኖራል።

ኢትዮጵያ በንጹሃን ደም እየታጠበች የምታሳልፈው እያንዳንዱ ቀን ታሪካዊ ጠባሳ ሆኖ ይቆያል። ዛሬ በአሰኮ ወረዳ የፈሰሰው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ደም የጋራ ሕመማችን ሊሆን ይገባል። መንግሥት ከፖለቲካዊ መግለጫዎች ወጥቶ የዜጎችን ደህንነት የማስከበር ቀዳሚ ኃላፊነቱን በአስቸኳይ ሊወጣ ይገባል፤ ካልሆነ ግን ታሪክና ትውልድ፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ የፈጣሪ ፍርድ ፊት መቆሚያ ማጣቱ አይቀሬ ነው።

ያሳዝናል... እጅግ ያሳዝናል! ለሟቾች ዘላለማዊ እረፍትን፣ ለተጎዱት መጽናናትን፣ ለሀገራችን ደግሞ ማስተዋልን ይስጥልን።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ