አምዶች
የቅርብ ዜና
አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ በሃይማኖት ጉዳዮች እና ሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሙሉ መግባባት ተደረሰ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ የአንበሳ ባንክ ሙሉ በሙሉ አዲስ የዳይሬክተሮች ቦርድ መረጠ የመንግሥት “ዜሮ ተፈናቃይ” መርሐግብር እና የተሸፈኑ እውነታዎች የአሜሪካ በግብፅ ላይ ያተኮረ አካሄድ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂ እያበላሸው ነው — ብሌን ማሞ ዲሪባ አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ በሃይማኖት ጉዳዮች እና ሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሙሉ መግባባት ተደረሰ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ የአንበሳ ባንክ ሙሉ በሙሉ አዲስ የዳይሬክተሮች ቦርድ መረጠ የመንግሥት “ዜሮ ተፈናቃይ” መርሐግብር እና የተሸፈኑ እውነታዎች የአሜሪካ በግብፅ ላይ ያተኮረ አካሄድ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂ እያበላሸው ነው — ብሌን ማሞ ዲሪባ
ዜና / ዜና ትንታኔ

ኤርትራ የትግራይን ክልል የአዲሱ የውክልና ጦርነት ቀጠና ለማድረግ እያካሄደች ያለው የፖለቲካ ቁማር

በያፌት ግርማ | August 6, 2026
🔒 Log in or create an account to earn rewards for reading this article!

በአፍሪካ ቀንድ አዲስ እና አደገኛ የፖለቲካ እንዲሁም የደህንነት ውጥረት እየያንዣበበ መሆኑን የሚጠቅሱ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች፣ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚታየው ስጋት ትግራይን የአዲስ የውክልና ጦርነት ቀጠና ለማድረግ ከተወጠነ ሰፊ ቀጠናዊ ሴራ ጋር የተያያዘ መሆኑን ገለጹ።

እንደ ክልላዊ ተንታኞች ገለጻ፣ የኤርትራው ኢሳይያስ አፈወርቂ መንግሥት በለመደው የውክልና ኃይሎች የመጠቀም ስልት፣ የታገደውን የሕወሓት ስብስብ እንደ መሳሪያ በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማወክ፣ ስትራቴጂካዊ የበላይነቷን ለማዳከም እና ቀጠናውን የማያቋርጥ የግጭት አዙሪት ውስጥ ለማስገባት እየሰራ ይገኛል።

በቅርቡ ፅምዶ በተሰኘው ኢትዮጵያን የሚቃወም ጥምረት ስም የኤርትራው ስርዓት የታገደውን የሕወሓት ቡድን በውክልና በመጠቀም በኢትዮጵያ ላይ ድጋሚ ጦርነት ለማንሳት እና ትግራይን የቀጠናው የጦርነት ጋሻ ለማድረግ እየሰራ መሆኑ ተመልክቷል። ይህም ተራ የፖለቲካ አሰላለፍ ሳይሆን፣ ትግራይን ወታደራዊ በማድረግ ወደ አውዳሚ ግጭት የመመለስ የተቀናጀ ስትራቴጂ እንደሆነ ተገልጿል።

በሌላ በኩል፣ የሕወሓት አክራሪ ስብስብ በበኩሉ ወጣቱን በፈቃደኝነት ማሰለፍ ባለመቻሉ፣ ህፃናትን ጨምሮ በኃይል እና በአስገዳጅ ሁኔታ ለወታደራዊ ስልጠና እየመለመለ ይገኛል። ይህም የቡድኑን የፖለቲካ ባዶነት እና ከሰላም እንዲሁም ከመልሶ ግንባታ ይልቅ ወደ ጦርነት ያደላ አቋሙን የሚያሳይ እንደሆነ የክልሉ የፖለቲካ አመራሮች ይጠቅሳሉ።

የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ቡድኑ በዜጎች ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍ፣ እገታ፣ ወጣቶችን በኃይል የመልመል እና የተቃወሙ ወላጆችን የማሰርና የማንገላታት ድርጊት በአደባባይ ኮንነዋል።

በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው የትግራይ የሰላም እና የለውጥ መድረክ በሰጠው መግለጫ እና ባዘጋጀው ህዝባዊ ሰልፍ "እገታው ይቁም፣ አስገዳጅ ምልመላ ይብቃ፣ ሰላም ለትግራይ" የሚሉ መፈክሮችን በማንገብ፣ ህዝቡ በቃኝ ማለቱን አሳይቷል።

የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገብሩ አስራት በበኩላቸው፣ የታገደው የሕወሓት ቡድን የውጭ ሀይሎችን ፍላጎት የሚያስፈጽም የትሮጃን ፈረስ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን እና የኢትዮጵያን ብሄራዊ አንድነት ለማዳከም ከሚሰሩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር መጣመሩን ተናግረዋል።

ይህ አዲስ ስጋት በህዳር ፪ሺህ፲፭ ዓመተ ምህረት በፕሪቶሪያ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተሉት እና ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ