አምዶች
የቅርብ ዜና
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ወደ 50 ሚሊዮን እየተቃረበ መሆኑ ተገለፀ አሜሪካ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ጥረትን ስትደግፍ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በስምምነቱ ሂደት መዘግየት ላይ ያለውን ቅሬታ ገለጸ በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ አዳማ እርሻ መሳሪያዎች ኢንዱስትሪ ከፍተኛ የንብረት ዘረፋ መፈጸሙ ተገለጸ አሜሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ አጋሮቿ በነዳጅ ንግድ የኃይል ሚዛኑን በኢራን ላይ እንዴት እንደቀየሩት አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ወደ 50 ሚሊዮን እየተቃረበ መሆኑ ተገለፀ አሜሪካ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ጥረትን ስትደግፍ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በስምምነቱ ሂደት መዘግየት ላይ ያለውን ቅሬታ ገለጸ በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ አዳማ እርሻ መሳሪያዎች ኢንዱስትሪ ከፍተኛ የንብረት ዘረፋ መፈጸሙ ተገለጸ አሜሪካ እና የመካከለኛው ምስራቅ አጋሮቿ በነዳጅ ንግድ የኃይል ሚዛኑን በኢራን ላይ እንዴት እንደቀየሩት አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ
ፖለቲካ / ዲፕሎማሲ

አሜሪካ የአፍሪካ ህብረት የሰላም ጥረትን ስትደግፍ፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በስምምነቱ ሂደት መዘግየት ላይ ያለውን ቅሬታ ገለጸ

በያፌት ግርማ | August 25, 2026
🔒 Log in or create an account to earn rewards for reading this article!

ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ያልተጠበቀ ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ወደ መቐለ አምርተዋል። ይህ ድንገተኛ ጉብኝት የፕሪቶሪያውን የጠላትነት ማቆም ስምምነት አፈጻጸም ለማስቀጠል የሚደረገውን ዓለም አቀፍ ጥረት የሚያሳይ ቢሆንም፡ በሌላ በኩል በአካባቢው አመራሮች ዘንድ በሰላም ሂደቱ መዘግየት ምክንያት እየጨመረ የመጣውን ቅሬታ አጉልቶ አሳይቷል።

​የአሜሪካው አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ እና የአፍሪካ ህብረት የአሜሪካ ልዑክ ቻርጅ ዲፌር ዋልተር ፓርስ በጋራ ባወጡት መግለጫ የኦባሳንጆን የዲፕሎማሲያዊ ጥረት አክብረው የተቀበሉ ሲሆን፡ የአፍሪካ ህብረት የሰላም እቅድን ማስፈጸም አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተውበታል። አሜሪካውያን ዲፕሎማቶች አካባቢው በከባድ ድርቅ እየተፈተነ ባለበት በዚህ ወቅት የነዋሪዎችን ስጋት ማቃለል እና ተፈናቃዮችን በክብር ወደ ቀያቸው መመለስ ዋና ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን በመግለጽ ወገኖች ለድርድር እና ለስምምነት ዝግጁ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

​በሌላ በኩል ከተግራይ ፕሬዝዳንት ፕሬስ ሴክሬተሪያት ጽህፈት ቤት የወጣው መግለጫ በጉብኝቱ ውጤት ላይ ያለውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል። ክልላዊ አመራሩ የኦባሳንጆን ያልተጠበቀ የጉብኝት ፕሮግራም አስተናግዶ ውይይት ቢያደርግም፡ ቀደም ሲል በሰኔ ወር ከተደረጉ ውይይቶች በኋላ ከፌደራል መንግስት በኩል የተሰጠ አዲስ ሀሳብ ወይም የታየ ተጨባጭ ወጤት አለመኖሩን አስታውቋል።

​በትግራይ አመራሮች በኩል ከቀረቡት ዋና ዋና ጥያቄዎች መካከል በትግራይ ላይ የተጣለው ኢኮኖሚያዊ እገዳ እና ከበባ በአስቸኳይ እንዲነሳ፡ የወታደራዊ ከበባ እንዲያበቃ እና የጸጥታ ስጋቶች እንዲረግቡ ማድረግ ይገኙበታል። በተጨማሪም የተያዙ ቦታዎችን ወደ ነበሩበት መመለስ፡ ተፈናቃዮችን በክብር ማቋቋም እና የትግራይ ህዝብ ነጻነት ግንባርን (ህወሓት) ህጋዊ እና ፖለቲካዊ ህልውና መስጠት የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

​የትግራይ አስተዳደር ውጤት አልባ የሆኑ ተደጋጋሚ ሂደታዊ ውይይቶች አሰልቺ መሆናቸውን ቢገልጽም፡ ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በተደገፈ፡ ግልጽ መዋቅር ባለው እና በጊዜ ገደብ በሚመራ የሰላም ውይይት ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጧል። የአሜሪካ ዲፕሎማቶችም በበኩላቸው በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ከኦባሳንጆ ጋር አብረው ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ