አምዶች
የቅርብ ዜና
አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ በሃይማኖት ጉዳዮች እና ሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሙሉ መግባባት ተደረሰ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ የአንበሳ ባንክ ሙሉ በሙሉ አዲስ የዳይሬክተሮች ቦርድ መረጠ የመንግሥት “ዜሮ ተፈናቃይ” መርሐግብር እና የተሸፈኑ እውነታዎች የአሜሪካ በግብፅ ላይ ያተኮረ አካሄድ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂ እያበላሸው ነው — ብሌን ማሞ ዲሪባ አብን የሀገራዊ ምክክር ሂደቱን አዎንታዊ ጎኖች ማደነቁንና የታዩ ጥሰቶችን መቃወሙን ገለጸ በግብፅ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጣቢያ ግንባታ ላይ ጉድለት መገኘቱ ውዝግብ አስነሳ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሰን ላይ ያላትን ይዞታ እያጣች መሆኑ ተገለጸ ደቡብ ኮሪያ ወታደራዊ ልምምዱ «እንደታቀደው ይቀጥላል» ስትል የትራምፕን ሃሳብ ውድቅ አደረገች የአዲስ አበባ ባለቤትነት ውዝግብ፡ በሀገራዊ ምክክሩና በፖለቲካው መድረክ ትልቅ አጀንዳ ሆኖ ቀጥሏል የጋራ ማረጋገጫ ቡድን አባላት ምርጫና የአሰራር ደንቦች አዲስ ውዝግብ ማስነሳታቸው ተገለፀ በሃይማኖት ጉዳዮች እና ሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሙሉ መግባባት ተደረሰ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ የአንበሳ ባንክ ሙሉ በሙሉ አዲስ የዳይሬክተሮች ቦርድ መረጠ የመንግሥት “ዜሮ ተፈናቃይ” መርሐግብር እና የተሸፈኑ እውነታዎች የአሜሪካ በግብፅ ላይ ያተኮረ አካሄድ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ስትራቴጂ እያበላሸው ነው — ብሌን ማሞ ዲሪባ
ፖለቲካ / ዲፕሎማሲ

ኢትዮጵያ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ዜጎቿ ደኅንነት እንዲጠበቅ ጠየቀች

በያፌት ግርማ | July 2, 2026
🔒 Log in or create an account to earn rewards for reading this article!

የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደዔታ አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ፣ በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ደኅንነት ዙሪያ በአዲስ አበባ ከደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኖንኬባ ሎሲ ጋር ትናንት በጽሕፈት ቤታቸው ተወያዩ። ይህ ውይይት የተካሄደው በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ የተለያዩ አካባቢዎች በውጭ ዜጎች፣ በተለይም በኢትዮጵያዊያን ፍልሠተኞች እና ነጋዴዎች ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶች ማገርሸታቸውን ተከትሎ ነው።

ሚንስትር ደዔታ ብርሃኑ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት፣ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚፈጸሙ ተደጋጋሚ ጥቃቶች እና የማንገላታት ድርጊቶች የኢትዮጵያን መንግሥት በእጅጉ አሳስበውታል። የዜጎች ደኅንነት መከበር ለኢትዮጵያ መንግሥት ቀዳሚ ተግባር መሆኑን የጠቆሙት አቶ ብርሃኑ፣ መሰል ጥቃቶች በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ታሪካዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳያሻክሩ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

"በቅርቡ በውጭ ዜጎች እና በወገኖቻችን ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶች እጅግ አሳሳቢ ናቸው" ያሉት ሚንስትር ደዔታው፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት የኢትዮጵያዊያንን ደኅንነት ለመጠበቅ እና መሰል ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ጠንካራ እና ተግባራዊ እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርበዋል። በተለይም በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ንብረት እንዳይዘረፍ እና ህይወታቸው አደጋ ላይ እንዳይወድቅ የጸጥታ አካላት ጥበቃ እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።

አምባሳደር ኖንኬባ ሎሲ በበኩላቸው፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ማንኛውንም ዓይነት የጥላቻ ጥቃት እና የሕግ ጥሰት በጽኑ እንደሚያወግዝ ገልጸዋል። መንግሥታቸው ጥቃቱን "ከደቡብ አፍሪካ እሴቶች ጋር የሚቃረን" ሲል መግለጹን ያስታወሱት አምባሳደሯ፣ በአሁኑ ወቅት ጥቃቱን በፈጸሙ አካላት ላይ ሰፊ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።

አምባሳደሯ አክለውም፣ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንና የምርመራው ውጤት እንደተጠናቀቀ በይፋ ለኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚያጋሩ ቃል ገብተዋል። በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ ሁለቱም ወገኖች የዜጎችን መብት ለማስከበር እና ቀጣናዊ ሰላምን ለማስጠበቅ በዲፕሎማሲያዊ እና በጸጥታ ዘርፎች በቅርበት ለመስራት ተስማምተዋል።

Recommended
Bottom Advertisement
Learn More

ተጨማሪ ዜናዎችን ያንብቡ

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ